” አሁንም ከእስር ያልተለቀቁ ሰዎች በአፋጣኝ ከእስር ይለቀቁ ” – ኢሰመኮ

0
0 0
Read Time:33 Second

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየካቲት 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተለይ በሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ እንዲነሳ መወሰኑን ኮሚሽኑ በበጎ መመልከቱን ገልጿል።

ኮሚሽኑ በአስቸኳይ ሁኔታ ወቅት ከአዋጁ አተገባበር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር የዋሉ እና አሁንም ያልተለቀቁ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ በድጋሚ አሳስቧል።

በተጨማሪ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቁጥጥር ስር ውለው የተለቀቁ ሰዎችም በእስር ስለመቆየታቸው ማረጋገጫ ባለማግኘታቸው ወደ ስራ መመለስ አለመቻልን ጨምሮ ለተለያዩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መጋለጣቸውን ባደረገው ክትትል መገንዘቡን ኮሚሽኑ ገልጿል።

ስለሆነም ሰዎች በእስር የቆዩበትን ጊዜ ማስረጃ እና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች የመስጠቱን ሂደት እንዲፋጠንና ሰዎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው መመለስ እንዲችሉ እንዲደረግ ኢሰመኮ አሳስቧል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *