ኦባሳንጆ ትላንት መቐለ ነበሩ።

0
0 0
Read Time:30 Second

የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ትላንት ትግራይ ክልል መቐለ ከተማ እንደነበሩ EFE Noticias ዘግቧል።

ኦባሳንጆ ወደትግራይ ክልል መቐለ የተጓዙት ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ ነው።

በመቐለ ቆይታቸው ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር ውይይት ማድረጋቸው እና ውይይቱም ጥሩ የሚባል እንደነበር ተሰምቷል።

የTPLF ቃልአቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ መቐለ እንደነበሩ አረጋግጠዋል ፤ ጉዟቸው ለቀውሱ ሰላማዊ መፍትሄ የመፈለግ ተልዕኮ አካል ነው ብለዋል። እሳቸው የመጡበት አውሮፕላን ተነስቶ እንደበረረ ግን የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል ሲሉ ክስ አሰምተዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም እና ሰላም እንዲወርድ መፍትሄ እያፈላለጉ ያሉት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ከዚህ ቀደምም ወደ ትግራይ ክልል ተጉዘው እንደነበር አይዘነጋም። 

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *