27 የክልል እና የተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ድምጽ የሚሰጠው ጷግሜ 01 ቀን 2013 ዓ.ም ይሆናል፡፡

0
0 0
Read Time:46 Second

ምርጫ2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች አስመልክቶ ትላንት መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። ዛሬ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።

በዚህም በተለያዩ ምክንያቶች ሰኔ 14 ድምጽ መስጠት የማይቻልባቸው አካባቢዎችን ገልጿል። በእነዚህ አከባቢዎች ምርጫው ጳጉሜ 1 የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።

እነዚህም፦

– ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል – መተከል፣ ሺናሻ ልዩ፣ ካማሽ እና ዳለቲ

– በኦሮሚያ ክልል -ቤጊ፣ ሰኞ ገበያ፣ አያና፣ገሊላ፣አሊቦ፣ጊዳሚ፣ ኮምቦልቻ

– አማራ ክልል-ማጀቴ (ማኮይ)፣ አርጎባ ልዩ፣ ሸዋሮቢት፣ ኤፌሶን፣ ጭልጋ 1፣ ጭልጋ 2፣ ላይ አርማጭ፣ አንኮበር

– ደ/ብ/ብ/ህ ክልል – ሱርማ ልዩ ፣ ዲዚ ልዩ፣ ቀይ አፈር መደበኛ፣ ማጀት መደበኛ፣ ሸኮ ልዩ፣ ቴፒ

– ሐረሪ ክልል – ጀጎል ልዩ ፣ ጀጎል መደበኛ ናቸው።

በተጨማሪም የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን አስመልክቶ በፍጥነት ህትመት ሊከናወንባቸው የሚችልባቸውን መንገዶችን በመፈለግ ትላንት አስታውቆት የነበረውን 32 የምርጫ ክልሎች ወደ 27 ዝቅ ማለቱን ገልጿል።

በዚህም መሰረት በነዚህ 27 የክልል እና የተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ድምጽ የሚሰጠው ከላይ በተጠቀሰው ጷግሜ 01 ቀን 2013 . ይሆናል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *