የኢትዮጵያ የሃገራዊ የውይይት መድረክ ግምገማ
መግቢያ ሃገራዊ የውይይት /National Dialogue/ መድረክ በተለያዩሃገራት ተከናውኗል ነገር ግን ውጤታማ የሆነው እፍኝበማይሞሉ አገራት ነው። ለምሳሌ ያህል በሩዋንዳ “በሁቱና ቱትሲ” የዘር ጭፍጨፋ ፣በሳውዝ አፍሪካ” አፓርታይድ አገዛዝንና ኤንሲ/ANC/” ፣ ላይቤሪያ ፣ በኬኒያው የምርጫ ወቅት የተነሳው ግጭትወ.ዘ.ተ. የተከወኑ አገራዊ ምክክሮች /Public Dialogues/በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው። ከላይ ከጠቀስኳቸው የምክክር መድረኮች የተዋጣለትና በስኬት የተጠናቀቀው የሩዋንዳው “ቱትሲና ኡቱ” ድርድር ነበር። የተቀሩት ግን የሚጠበቅባቸውን የድርድር ስርአትና አካኤድ ስላልተከተሉ ውጤታማ አልሆኑም። የተፈፀመው...
