ሕወሓት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢብርቱካን ሚደቅሳን ገፍቶ ጣላት? ወይስ እውን ታማለች።

0
0 0
Read Time:1 Minute, 33 Second

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደድቅሳ
በሕወሓት ጉዳይ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስታወቁ

ብርቱካን ሚደቅሳ በተረጋገጠው የግል የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ይፋ እንዳደረጉት ከነሐሴ 01/2015 ዓ.ም. ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነት ኃላፊነታቸው ለመልቀቅ ሰኔ 05/2015 ዓ.ም. ለሕዝብ ምክር ቤት አፈጉባኤ አሳውቀዋል።

በታኅሣሥ 2011 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ በመሆን ሥራውን የተረከቡት ብርቱካን፣ ከአራት ዓመታት በላይ በኃላፊነቱ ላይ ቆይተው በቦርዱ ውስጥ ለውጦች እንዲካሄዱ አድርገዋል።

ብርቱካን ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸውን በተመለከተ ይፋ ባደረጉበት መልዕክታቸው ላይ በሰብሳቢነታቸው ዘመን ሦስት ሕዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን ማካሄዳቸውን ጠቅሰዋል።

“የተሰጡኝን ኃላፊነቶች ሕጋዊነት፣ ፍትሃዊነት እና ቅንነትን በተከተለ ሁኔታ ለማከናወን ስጥር ቆይቻለሁ” በማለት ጤናቸውን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት ስለሚያስፈልጋቸው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ መወሰናቸውን ገልጸዋል።

ብርቱካን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢነታቸውን ከነሐሴ መጀመሪያ አንስቶ ለመልቀቅ በመወሰናቸው በሚቀጥሉት አርባ ቀናት “ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን የማጠናቀቅ እና አስተዳደራዊ ሽግግር የመፈፀም ኃላፊነቶችን የምወጣበት ይሆናል” ብለዋል።

ጨምረውም ብርሔራዊ ምርጫ ቦርድን በሰብሳቢነት ለመምራት በዕጩነት ያቀረቧቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን እና ኃላፊነቱን ለሰጣቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ብርቱካን ሚደቅሳ ባለፈው ሳምንት ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በአሁኑ ወቅት በጊዜያዊ አስተዳደር ስር በምትገኘው ትግራይ ውስጥ አስቸኳይ ምርጫ ለማካሄድ አመቺ ሁኔታ እንደሌለ ገልጸዋል።

የጤና ጉዳይን የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነታቸውን ለመልቀቅ ምክንያት እንደሆናቸው ያመለከቱት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ በዳኝነት ዘመናቸው የቀድሞው የህወሓት ባለሥልጣን የነበሩትን አቶ ስዬ አብረሃን በተመለከተ ያሳለፉት የፍርድ ውሳኔ ዝናን እንዳስገኘላቸው ይታወሳል።

ብርቱካን ሚደቅሳ በአወዛጋቢው የ1997 ዓ.ም. ምርጫ ወቅት የዋነኛው ተቃዋሚ ፓርቲ የቅንጅት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል የነበሩ ሲሆን፣ በፓርቲው ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ ነበሩ።

የምርጫውን ውዝግብ ተከትሎ መንግሥት የተቃዋሚ አመራሮችን እና ጋዜጠኞችን ለእስር በዳረገበት ጊዜ ብርቱካንም በእስር ላይ ቆይተው ነበር።

ቅንጅት ከፈረሰ በኋላም አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ የተሰኘ ፓርቲን ከሌሎች አጋሮቻቸው ጋር በመመሥረት በፖለቲካው ውስጥ ለመቆየት የሞከሩ ቢሆንም ብዙም ሳይቆዩ ድጋሚ ለእስር ተዳርገዋል።

ብርቱካን በአገሪቱ ውስጥ የነበረው የተቃውሞ ፖለቲካ መድረክ እየጠበበ በመምጣቱ፣ በገዢው የኢህአዴግ መንግሥት በገጠማቸው ጫና እና እስር ወደ አሜሪካ በስደት ሄደው በትምህርት ላይ ለዓመታት ከቆዩ በኋላ ነበር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጥሪ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሆኑ የተሾሙት።

Source: Alebachew

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *