1 0
Read Time:31 Second


የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት የድሮው የአፍሪካ አንድነት ግንቦት 16 ቀን 1955 ዓ.ም በአዲስ አበባ መመስረቱ ጋር ተያይዞ አብሮ የተከፈተው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ላይ የመጀመሪያ ሴት ዜና አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሊኔ መኩሪያ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው ቤታቸው ህይወታቸው እንዳለፈ ፊደል ፖስት ዘግቧል።

የሶስት ሴት ልጆች እናት የሆኑት ወይዘሮ እሌኒ በብስራተ ወንጌል ራዲዮ (በኋላ የአብዮታዊት ኢትዮጵያ ድምጽ) ፣በወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማሕበር (ወሴክማ) የሰሩ ሲሆን እንዲሁም ፍራንሲስ ፋልሴቶ ላሳተማቸው “ኢትዮፒክ” አልበሞች ፕሮዲውሰር ነበሩ።

በቢቢሲ አንግሊዘኛ የሰሩም ሲሆን በኢትዮጵያም ሬድዮ ” ሊስነርስ ቾይስ ” በተባለው የእንግሊዘኛ ዘፈን ፕሮግራም ላይ አዘጋጅ ሆነው ሰርተዋል።

በአሜሪካ ሀገር የነርስ ሙያ የተማሩ ሲሆን በሳንፎርድ ት/ቤት ደግሞ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተምረዋል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *