የሱዳን የሉዓላዊ ም/ቤት ሊቀመንበር ፤ ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን ባህር ዳር የጣና ፎረም እየተካፈሉ ይገኛሉ።

Read Time:44 Second
ባህር ዳር የጣና ፎረም መካሄድ ጀምሯል።
10ኛው የ ” ጣና ፎረም ” ጉባኤ በአፍሪካ የሰላም ፣ ጸጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክ ይነግራል እስከ ጥምቅት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
በ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው ሥብሰባ የሶማሊያ ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ እና የሱዳን የሉዓላዊ ም/ቤት ሊቀመንበር ፤ ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን እና ሌሎችም እየተካፈሉ ይገኛሉ።
ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ ” በአፍሪካውያን ለአፍሪካውያን የሚጠቅሙ መፍትሔዎች የሚወጡበት ውጤታማ የውይይት ጊዜ እንደሚሆንልን እምነቴ ነው ” ብለዋል።
የጣና ፎረም አፍሪካውያን መሪዎችን እና ባለ ድርሻ አካላትን በአሕጉራዊ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በማወያየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመቀየስ አልሞ ሚካሄድ ውይይት መሆኑን ጠቅላዩ ገልፀዋል።
በሌላ በኩል ፤ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን የሽግግር መንግስት ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ከሆኑት ሌተናል ጀነራል አል ቡርሃን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል ፤ ከዚህ በተጨማሪ ዓባይ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለውን ግዙፍ የድልድይ ግንባታ ስራ ጎብኝተዋል።
- Ethiopian PM’s Easter Messages: Balancing Faith, Politics, and Secular Governance
- Amnesty International’s Call to Halt Ethiopia’s Corridor Development Project: A Crisis of Rights vs. “Progress”
- PM Abiy Ahmed’s Appointment of Getachew Reda as Ministerial Advisor
- Ethiopian Prime Minister might maneuver to remain in power for additional 18 years!
- Foreign Direct Investment (FDI) in Ethiopia Contrasting Perspectives on China’s Dominance, EU Engagement, and U.S. Opportunities