የሱዳን የሉዓላዊ ም/ቤት ሊቀመንበር ፤ ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን ባህር ዳር የጣና ፎረም እየተካፈሉ ይገኛሉ።
Read Time:44 Second
ባህር ዳር የጣና ፎረም መካሄድ ጀምሯል።
10ኛው የ ” ጣና ፎረም ” ጉባኤ በአፍሪካ የሰላም ፣ ጸጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክ ይነግራል እስከ ጥምቅት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
በ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው ሥብሰባ የሶማሊያ ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ እና የሱዳን የሉዓላዊ ም/ቤት ሊቀመንበር ፤ ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን እና ሌሎችም እየተካፈሉ ይገኛሉ።
ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ ” በአፍሪካውያን ለአፍሪካውያን የሚጠቅሙ መፍትሔዎች የሚወጡበት ውጤታማ የውይይት ጊዜ እንደሚሆንልን እምነቴ ነው ” ብለዋል።
የጣና ፎረም አፍሪካውያን መሪዎችን እና ባለ ድርሻ አካላትን በአሕጉራዊ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በማወያየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመቀየስ አልሞ ሚካሄድ ውይይት መሆኑን ጠቅላዩ ገልፀዋል።
በሌላ በኩል ፤ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን የሽግግር መንግስት ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ከሆኑት ሌተናል ጀነራል አል ቡርሃን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል ፤ ከዚህ በተጨማሪ ዓባይ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለውን ግዙፍ የድልድይ ግንባታ ስራ ጎብኝተዋል።
- The Abraham Accords: The Force Re‑shaping the Gulf–Red Sea–Horn Energy & Geopolitical Architecture (Part II)
- The Abraham Accords: The Force Re‑shaping the Gulf–Red Sea–Horn Energy & Geopolitical Architecture (Part I)
- WHEN TEWODROS SINGS, ETHIOPIA LISTENS AND THE PALACE TREMBLES
- Pictures, Pejorative Discourse, and the “Ape” Insult
- The Oldest Trick in the World
