Read Time:44 Second
ባህር ዳር የጣና ፎረም መካሄድ ጀምሯል።
10ኛው የ ” ጣና ፎረም ” ጉባኤ በአፍሪካ የሰላም ፣ ጸጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክ ይነግራል እስከ ጥምቅት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
በ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው ሥብሰባ የሶማሊያ ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ እና የሱዳን የሉዓላዊ ም/ቤት ሊቀመንበር ፤ ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን እና ሌሎችም እየተካፈሉ ይገኛሉ።
ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ ” በአፍሪካውያን ለአፍሪካውያን የሚጠቅሙ መፍትሔዎች የሚወጡበት ውጤታማ የውይይት ጊዜ እንደሚሆንልን እምነቴ ነው ” ብለዋል።
የጣና ፎረም አፍሪካውያን መሪዎችን እና ባለ ድርሻ አካላትን በአሕጉራዊ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በማወያየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመቀየስ አልሞ ሚካሄድ ውይይት መሆኑን ጠቅላዩ ገልፀዋል።
በሌላ በኩል ፤ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን የሽግግር መንግስት ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ከሆኑት ሌተናል ጀነራል አል ቡርሃን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል ፤ ከዚህ በተጨማሪ ዓባይ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለውን ግዙፍ የድልድይ ግንባታ ስራ ጎብኝተዋል።
- The Architecture of Collapse: Ethiopia’s Convergent Crises and the Question of Civilisational Survival
- The Abraham Accords: Part 4 Concludes a Strategic Reckoning
- From Mandela’s Ethiopian Trainer to Today’s Xenophobic Violence
- When Democracy Weakens: Fragile Political Cultures and Fascistic Drift
- The Abraham Accords: The Force Re‑shaping the Gulf–Red Sea–Horn Energy & Geopolitical Architecture (Part III)
