የመንግስት አካላት ሕግ ሲጣስ የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆነው በመገኘታቸው እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው ብላለች

0
0 0
Read Time:57 Second

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፤ መንግስትበሃይማኖት መካከል ጣልቃ አልገባም “/” ገለልተኛ ነኝየሚሉ ንግግሮችን እና ሃሳቦችን ቢያራምድም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ከዚህ ፍፁም ተቃራኒ መሆኑን እየገለፀች ትገኛለች።

ቤተክርስቲያን ህገወጥ ናቸው ብላ ያወገዘቻቸው አካላት የመንግስትን የፀጥታ አካላትን ሽፋን እያገኙ፤ የቤተክርስቲያን ስርዓትም በከፍተኛ ሁኔታ እየተጣሰ መሆኑን ገልፃለች።

ቅዱስ ሲኖዶስ፤ በተለያዩ ክልሎች እና የፌዴራል መንግሥት በሚመራቸው ቦታዎች ውስጥ በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ አህጉረ ስብከት የሆኑትን ሥርዓተ አምልኮዋን የምትፈጽምባቸው በየመዋቅሩ የሚገኙ አስተዳደር ቢሮዎችን  ከሕግ አግባብ ውጭ የቤተ ክርስቲያኗ እምነት ተከታይ ያልሆኑ ግለሰቦችን በማካተት በመንግሥት ልዩ ኃይል ድጋፍ በመውረር እና በመስበር የሕግ አግባብነት በሌላቸው እንዲሁም መብት እና ጥቅም ሳይኖራቸው በማሸግ ቤተ ክርስቲያን ላይ ወረራ እየተፈጸመባት ይገኛል ብሏል።

በሻሸመኔ የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ የሰው ህይወት ጠፍቷል፣ ጉዳት ደርሷል።

በጭሮ/ ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእመናን መወርወራቸውና ተኩስ ከፍተው እንደበር ቤተክርስቲያና ገልጻለች።

ዛሬ በጭሮ ምእመናን ከጠዋት ጀምረው ቤተ ክርስቲያኗን ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን የዞኑ የጸጥታ ኃይል “በሁለታችሁ አንገባም” በማለት ገለልተኛ ለመሆን ሞክሮ ውሏል። ነገር ግን ምሽት ላይ ከክልል የመጣ ትእዛዝ ነው በሚል የክልሉ ልዩ ኃይልን ጨምሮ ተኩስ በመክፈት አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእምናን መወርወሩ ተገልጿል።

ቤተክርስቲያኗ የመንግስት አካላት ሕግ ሲጣስ የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆነው በመገኘታቸው እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው ብላለች።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *