መስከረም አበራ ዛሬ ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ በሜክሲኮ የፌደራል ወንጀል ምርመራ መታሰሯን ተገለጠ።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/12/img_2411.jpg?fit=640%2C359&ssl=1)
Read Time:31 Second
ከዚህ ቀደም ታስራ ከእስር የተፈታችው መስከረም አበራ ዛሬ ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር መዋሏን ባለቤቷ መናገሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
የመስከረም አበራ ባለቤት አቶ ፍጹም ገ/ሚካኤል እንደተናግረው ፤ ከሰዓት 10፡30 አካባቢ ” ሃያ ሁለት / 22 ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አብረው ሳሉ ሲቪል እና የፌደራል ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች መጥተው መስከረምን ይዘው ሄደዋል።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/12/img_2410.jpg?resize=640%2C432&ssl=1)
መስከረም የግለሰቦቹን ማንነት ስትጠይቅ የፌደራል ፖሊስ አባላት መሆናቸውን ከገለጹ በኋላ ሜክሲኮ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ መሥሪያ ቤት ይዘዋት እንደሚሄዱ ተናግረው በመኪና እንደወሰዷት ባለቤቷ ፍጹም ገ/ሚካኤል አስረድቷል።
ፍጹም እንደሚለው ባለቤቱ ታስራ ወደምትገኝበት ሜክሲኮ የፌደራል ወንጀል ምርመራ አቀንቶ መስከረምን ማግኘቱንና በምን ወንጀል ተጠርጥራ በቁጥጥር ስር እንደዋለች እንደማታውቅ ተናግረዋል።