ክቡር አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ ፓሪስ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ማህበረሰቡን በማመስገን ተሰናበቱ።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/12/img_2422.jpg?fit=640%2C336&ssl=1)
Read Time:23 Second
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/12/img_2423.jpg?resize=554%2C554&ssl=1)
በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ፖርቹጋል ፣ ሞናኮ እንዲሁም UNSECO #የኢትዮጵያ አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ የስራ ጊዜያቸውን እንዳጠናቀቁ አሳውቀዋል።
አምባሳደር ሄኖክ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰራጩት ፅሁፍ ፤ በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋል፣ ሞናኮ እና UNSECO በአምባሳደርነት ሀገራቸውን ያገለገሉበት የስራ ጊዜ ማብቃቱን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን በውጪ ሀገር ከወከል የበለጠ ትልቅ ነገር እንደሌለ የገለፁት አምባሳደር ሄኖክ ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ሀገራቸውን የማገልገል እድል ስላመቻቹላቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በተጨማሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ ፓሪስ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ማህበረሰቡን አመስግነዋል ፤ ሰላምና ብልፅግናን ለኢትዮጵያ ተመኝተዋል።