ዲና ሙፍቲ (አምባሳደር) “በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ዕርዳታ የሚሰጥባቸው መንገዶች መከፈታቸው ተገለጸ”

0
ዲና ሙፍቲ (አምባሳደር)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ (አምባሳደር) በትግራይ ክልል ‹‹የሕግ ማስከበር ሥራ›› ሲካሄድ የነበረው ወታደራዊ ዕርምጃ በመገባደዱ፣ የቀረው የፖሊስ ሥራ በመሆኑ፣ በአካባቢው ሰብዓዊ ዕርዳታ ለመስጠት የሚፈልጉ ድርጅቶች አገልግሎቱን ማቅረብ እንዲችሉ መንገዶች እንደተከፈቱላቸው አስታወቁ፡፡

0 0
Read Time:52 Second

ብሩክ አብዱ

በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ዕርዳታ የሚሰጥባቸው መንገዶች መከፈታቸው ተገለጸ


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ (አምባሳደር) በትግራይ ክልል ‹‹የሕግ ማስከበር ሥራ›› ሲካሄድ የነበረው ወታደራዊ ዕርምጃ በመገባደዱ፣ የቀረው የፖሊስ ሥራ በመሆኑ፣ በአካባቢው ሰብዓዊ ዕርዳታ ለመስጠት የሚፈልጉ ድርጅቶች አገልግሎቱን ማቅረብ እንዲችሉ መንገዶች እንደተከፈቱላቸው አስታወቁ፡፡

ቃል አቀባዩ ዓርብ ኅዳር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰጡት መግጫ እንዳስታወቁት፣ አሁን በሁሉም አካባቢዎች ለመንቀሳቀስ ለሚፈልጉ የሰብዓዊ ዕርዳታ የሚያደርጉ ድርጅቶች መንገዶችን በመክፈት እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ ተችሏል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባደረጉት ስምምነት መሠረት፣ የተመድ የሰብዓዊ ዕርዳታዎች ማስተባሪያ ቢሮ ወደ አካባቢው ተጉዞ የሰብዓዊ ዕርዳታ ፍላጎቶችን ለማወቅ የሚያስችሉትን ግምገማ አድርጓል ብለዋል፡፡ ይኼ ቡድን ያየውን በተመለከተም ሪፖርት ያዘጋጀ መሆኑንና ሪፖርቱም በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በትግራይ ክልል ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. መንግሥት በአገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መፈጸሙንና የጦር መሣሪያዎች ዝርፊያም ለማድረግ መሞከሩን በማስታወቅ፣ በትግራይ ክልል ወታደራዊ ዕርምጃ እንዲወሰድ ማዘዙን በወቅቱ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ጦርነቱ በተካሄደባቸው አራት ሳምንታት ውስጥ የመከላከያ ሠራዊቱ የትግራይ ክልል ዋና ከተማ የሆነችውን መቀሌን የተቆጣጠረ ሲሆን፣ በወንጀል ይፈለጋሉ የተባሉ ከ167 በላይ ግለሰቦችም እየተፈለጉ ናቸው፡፡

Source: https://www.ethiopianreporter.com

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *