0 0
Read Time:52 Second

አልቃይዳ በቀጣይ በማን ይመራል ?

አሜሪካ አልዛዋሂሪን ገደልኩኝ ማለቷን ተከትሎ አልቃይዳ የቀድሞውን የግብፅ ወታደር መሪ ያደርጋል ተብሎ ተገምቷል።

በአልቃይዳ ውስጥ ሶስተኛው ሰው ነው ተብሎ የሚታሰበው ሳይፍ አልአድል ሲሆን የቀድሞ ግብፅ ኮሎኔል ፣ በወታደራዊ እና በደህንነት ጉዳዮች ጥልቅ እውቀት እንዳለው ይነገራል።

ከዓመታት በፊት አልአደል ፤ በአፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን እና ሱዳን ላሉ የአልቃይዳ እና ሌሌች ቡድኖች አባላት እንዲሁም ፀረ-UN አቋም ላላቸው የሶማሊያ ጎሳዎች ወታደራዊ እና የስለላ ስልጠና መስጠቱ ይነገራል።

በሶማሊያ በኬንያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በራስ ካምቦኒ የአልቃይዳን ማሰልጠኛ ተቋምም መስርቷል።

አል-አደል በ1987 የግብፅን መንግስት ለመጣል ሞክሯል በሚል ተከሶ የነበረ ሲሆን ክሱ ውድቅ ከተደረገ በኋላ በ1988 አገሩን ለቆ የሶቪየትን የአፍጋኒስታን ወረራ ለመመከት ወደ አፍጋኒስታን አቅንቶ ነበር።

አልአደል ከዓመታት በፊት በሱዳን መዲና ካርቱም ውስጥም ለተመለመሉ ታጣቂዎች ፈንጂዎችን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ትምህርት ሲሰጥ እንደነበር እሱን በተመለከተ የተፃፉት መረጃዎች ያሳያሉ።

ከ1998ቱ በኬንያ ከአሜሪካ ኤምባሲ የቦንብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ (ከ200 በላይ ሰዎች ተገድለዋል) አሜሪካ በጥብቅ ከምትፈልጋቸው ሰዎች አንዱ ነው።

አሁን ላይ ብዙም ስለእሱ የሚታወቅ ትክክለኛ መረጀ የለም። ነገር ግን አልቃይዳ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለው ሲሆን ቀጣዩ መሪም ይሆናል ተብሎ የሚጠበቅ ሰው ነው።

መረጃው የተሰባሰበው ከአል ሲፋን የቀድሞ FBI ኤጀንት ነው።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *