ዶ/ር ደብረፅዮን ለሠላም ድርድር ድርጅታቸው ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2021/07/detsi.jpg?fit=640%2C316&ssl=1)
Read Time:37 Second
ህወሓት በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ትላንት ምሽት አሳውቋል።
ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ርጠኞች ነን ሲልም ገልጿል።
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለአፍሪካ ህብረት ሊቀንበር በፃፉት ደብደቤ ፤ ለሰላም ሂደቱ ይረዳል ያሉትን ” ግጭት ማቆም ” ዋናው የድርድሩ የአጀንዳው አካል ተደርጎ ስለመያዙ ጠይቀዋል።
” ተደራዳሪዎቻችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጁ ነን ” ሲሉም አሳውቀዋል።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/10/2022-10-06-05.46.33.jpg?resize=640%2C911&ssl=1)
” ግብዣው ቀደም ብሎ ያልተማከርንበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ቢሰጠን ” ሲሉ በፃፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
![](https://i0.wp.com/ethiopiantribune.com/wp-content/uploads/2022/10/45352dbd-308a-49a4-b69f-add2e540f71f.jpg?resize=640%2C834&ssl=1)
እነዚህም ፦
– በሰላም ውይይቱ ተጨማሪ ተዋናይን እንደ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎች ወይም ዋስትና ሰጪዎች የሚጋበዙ ይኖሩ እንደሆነ፤
– ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አይነት ሚናዎችን ሊሰጥ እንደታሰበ ፤
– ለተደራዳሪ ቡድኑ የሎጅስቲክስ ፤ #የጉዞ እና የደህንነት ዝግጅቶችን በተመለከተ እንዲብራራላቸው ዶ/ር ደብረፅዮን ለፋኪ በላኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
ዛሬ ጥዋት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በደቡብ አፍሪካ የሚደረገውን የሰላም ንግግር ግብዣ መቀበሉን ማሳወቁ ይታወቃል።