ዶ/ር ደብረፅዮን ለሠላም ድርድር ድርጅታቸው ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።

0
1 0
Read Time:37 Second

ህወሓት በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ትላንት ምሽት አሳውቋል።

ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ርጠኞች ነን ሲልም ገልጿል።

ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለአፍሪካ ህብረት ሊቀንበር በፃፉት ደብደቤ ፤ ለሰላም ሂደቱ ይረዳል ያሉትን ” ግጭት ማቆም ” ዋናው የድርድሩ የአጀንዳው አካል ተደርጎ ስለመያዙ ጠይቀዋል።

” ተደራዳሪዎቻችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጁ ነን ” ሲሉም አሳውቀዋል።

” ግብዣው ቀደም ብሎ ያልተማከርንበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ቢሰጠን ” ሲሉ በፃፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል።

እነዚህም ፦ 

– በሰላም ውይይቱ ተጨማሪ ተዋናይን እንደ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎች ወይም ዋስትና ሰጪዎች የሚጋበዙ ይኖሩ እንደሆነ፤

– ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አይነት ሚናዎችን ሊሰጥ እንደታሰበ ፤

– ለተደራዳሪ ቡድኑ የሎጅስቲክስ ፤ #የጉዞ እና የደህንነት ዝግጅቶችን በተመለከተ እንዲብራራላቸው ዶ/ር ደብረፅዮን ለፋኪ በላኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል።

ዛሬ ጥዋት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በደቡብ አፍሪካ የሚደረገውን የሰላም ንግግር ግብዣ መቀበሉን ማሳወቁ ይታወቃል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *